ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በሱጁዳቸው ወቅት እንዲህ እያሉ ዱዓእ ያደርጉ ነበር: "አላህ ሆይ ወንጀሌን ማረኝ" በመሸሸጊያህ ሸሽገኝ፤ ተከትሎት የሚመጣውን መከራንም ጠብቀኝ፤ ይቅር በለኝ፤ እለፈኝ (ሁሉንም) ማለትም (ደቂቁንም) ትንሹንም ጥቃቅኑንም፤ (ትልቁንም) ግዙፉንም ብዙውንም፤ (የመጀመሪያውንም) የመጀመሪያውን ወንጀሌንም፤ (የመጨረሻውንም) በነርሱ መካከል ያለውን ወንጀሌንም (ግልፁንም ድብቁንም) ከአንተ በቀር ማንም የማያውቀውን ወንጀሌንም ማረኝ።