ከአነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ ነቢይ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሳይሉን አንድም ኹጥባ አያደርጉም ነበር: "አማና (አደራ) የሌለው ሰው ኢማን የለውም፤ ቃልኪዳን የማያከብር የሆነ ሰው ሃይማኖት የለውም።"» حسن لغيره - አሕመድ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለው ተናገሩ: ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ኹጥባ ሲያደርጉ ወይም ሲመክሩ ሁለት ነገሮችን ሳይጠቅሱ የሚያልፉበት ጊዜ በጣም ጥቂት ጊዜያት ነው። የመጀመሪያው: አንድን አካል በገንዘብ ወይም በነፍስ ወይም በቤተሰብ ጉዳይ ነፍሱ ውስጥ ከዳተኝነት ያለችበት ሰው የተሟላ ኢማን የለውም። ሁለተኛው: ቃልኪዳንን የሚያፈርስ ሰው የተሟላ ሃይማኖት የለውም።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አደራን በመወጣት ላይና ቃልኪዳንን በመሙላት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። እነዚህን ሁለት ነገሮች ማፍረስ ኢማንን ያፈርሳል።
  • አደራን ከመካድና ቃልኪዳንን ከማፍረስ መከልከሉንና እነዚህን መፈፀምም ከትላልቅ ወንጀሎች እንደሆነ እንረዳለን።
  • ሐዲሡ በአላህና በባሪያው መካከል ያለንም ይሁን ፍጡራን እርስ በርሳቸው መካከል ያለውንም አደራ መጠበቅንና ቃልኪዳን ማክበርን ያካትታል።