አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለው ተናገሩ: ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ኹጥባ ሲያደርጉ ወይም ሲመክሩ ሁለት ነገሮችን ሳይጠቅሱ የሚያልፉበት ጊዜ በጣም ጥቂት ጊዜያት ነው። የመጀመሪያው: አንድን አካል በገንዘብ ወይም በነፍስ ወይም በቤተሰብ ጉዳይ ነፍሱ ውስጥ ከዳተኝነት ያለችበት ሰው የተሟላ ኢማን የለውም። ሁለተኛው: ቃልኪዳንን የሚያፈርስ ሰው የተሟላ ሃይማኖት የለውም።