ከኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: "እናንተ የምትፈልጉትን ምግብና መጠጥ እየተመገባችሁ አይደልንዴ? ነቢያችሁን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሆዳቸውን የሚሞሉበት የሆነ የወረደ ተምርን እንኳ ሳያገኙ ቀርተው ተመልክቻቸዋለሁ።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ኑዕማን ቢን በሺር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሰዎች ያሉበት ፀጋ የፈለጉትን ያህል የሚበሉና የሚጠጡበት ሁኔታ ላይ እንዳሉ ገልፀው ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ግን ረሃባቸውን ለማስታገስ ሆዳቸውን የሚሞላ የወረደ ተምርን እንኳ የማያገኙበት ሁኔታ ላይ እንደነበሩ ተናገረ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የነበሩበትን የዱንያ ዛሂድነት (ቸልተኝነት) መገለፁ።
  • ከዱንያ ዛሂድ (ቸልተኛ) በመሆን፣ ዱንያን በማሳነስና ነቢዩን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመከተል ላይ መነሳሳቱን እንመለከታለን።
  • ሰዎች ያሉበትን ፀጋ በማስታወስና አላህንም በማመስገን ላይ መተዋወስ እንደሚገባ መነሳሳቱን እንረዳለን።