ሰዕድ ቢን አቢ ወቃስ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - ራሱን በጀግንነትና በመሳሰሉት ምክንያት ከርሱ በታች ካሉ ደካማ ሰዎች የበለጠ አድርጎ አሰበ። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "በደካሞቻችሁ፣ በነርሱ ዱዓ፣ ሶላትና ኢኽላስ ካልሆነ በቀር ትረዳላችሁን? ትቀለባላችሁን?" አሉ። አብዛኛው ጊዜ ደካማዎች ዱዓቸውን እጅግ ለአላህ አጥርተው፣ አምልኳቸውንም እጅግ ተመስጠው ነው የሚፈፅሙት። ይህም ቀልባቸው በዱንያ ጌጣጌጥ ከመንጠልጠል የፀዳ ስለሆነ ነው።