ከሙስዐብ ቢን ሰዕድ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ሰዕድ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ከሌሎች ሰዎች የበለጠ ደረጃ እንዳለው ተሰማው። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉት: "የምትረዱትና የምትቀለቡት በደካሞቻችሁ ሰበብ አይደለምን?" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪ ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ሰዕድ ቢን አቢ ወቃስ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - ራሱን በጀግንነትና በመሳሰሉት ምክንያት ከርሱ በታች ካሉ ደካማ ሰዎች የበለጠ አድርጎ አሰበ። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "በደካሞቻችሁ፣ በነርሱ ዱዓ፣ ሶላትና ኢኽላስ ካልሆነ በቀር ትረዳላችሁን? ትቀለባላችሁን?" አሉ። አብዛኛው ጊዜ ደካማዎች ዱዓቸውን እጅግ ለአላህ አጥርተው፣ አምልኳቸውንም እጅግ ተመስጠው ነው የሚፈፅሙት። ይህም ቀልባቸው በዱንያ ጌጣጌጥ ከመንጠልጠል የፀዳ ስለሆነ ነው።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • በመተናነስ ላይ መነሳሳቱንና በሌሎች ላይ ከፍ ከፍ ከማለት መከልከሉን እንረዳለን።
  • ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ጠንካራው በጀግንነቱ ስለሚሻል ከደካሞች ቢበልጥ ደካማው ደግሞ በዱዓውና ስራውን ለአላህ አጥርቶ በመስራቱ ስለሚሻል ከጠንካራው ይበልጣል።"
  • ለድሃዎች በጎ በማድረግና ሐቃቸውን በመስጠት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። ይህን ማድረግህ አላህ እንዲያዝንልህና እንዲረዳህ የሚያደርግ አንዱ ምክንያት ነውና።