ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሰዎች ወደ ተቀማመጡበት ስፍራ የመጣ ሰው ሰላምታ እንዲያቀርብና መነሳትም የፈለገ ጊዜ የተቀማመጡትን ሰዎች በድጋሚ ሰላምታ እንዲያቀርብላቸው ጠቆሙ። በሚመጣበት ወቅት (ሲቀላቀላቸው) ያቀረበው የመጀመሪያው ሰላምታ በሚለያይበት ወቅት (ሲሰናበታቸው) ከሚያቀርበው የመጨረሻ ሰላምታ የበለጠ የሚያደርገው ነገር እንደሌለ ተናገሩ።