ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የሙስሊምን ሐቅ እያወቀ ያለአግባብ ለመውሰድ ዋሽቶ በአላህ ከመማል አስጠነቀቁ። የዚህ ተግባር ቅጣቱም እሳት መግባትና ጀነት መነፈግ ነው። ይህም ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል አንዱ ነው። አንድ ሰውዬም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! የተማለበት ነገር ትንሽ ብትሆን እንኳ?" አለ። ነቢዩም (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) "የወሰደው ለመፋቂያነት ከአራክ ዛፍ የሚወሰድ እንጨት እንኳ ብትሆን ይህን ቅጣት ይቀጣል።" አሉ።