ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ሰው ማንኛውንም ስራ መስራት እንዳለበትና ገመዱን ይዞ ጀርባው ላይ የሚሸከመውን እንጨት ሰብስቦ በገመዱ አስሮ በመሸጥ ካገኘው ገንዘብም መመገቡ ወይም መመፅወቱ ከሰዎችም መብቃቃቱና ከልመና ውርደት (በሰው ፊት ከመገረፍ) ፊቱን መጠበቁ ሰጡትም ከለከሉትም ሰዎችን ከመለመን የተሻለ እንደሆነ ገለፁ። ሰዎችን መለመን ውርደት ነው። አማኝ ደግሞ ቆፍጣና እንጂ ወራዳ አይደለም።