ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ግዴታ ሶላቶች ከተጠናቀቁ በኋላ እነዚህን ያለ ሰው የሚያገኘውን ምንዳ ገለፁ: ሰላሳ ሶስት ጊዜ "ሱብሓነላህ": ይህም አላህን ከጉድለቶች ሁሉ ማጥራት ነው። ሰላሳ ሶስት ጊዜ "አልሐምዱ ሊላህ": ይህም አላህን ከመውደድና ከማላቅ ጋር በምሉዕ ባህሪያቱ ማወደስ ነው። ሰላሳ ሶስት ጊዜ "አላሁ አክበር": ማለት ይህም አላህ ከሁሉም ነገር እጅግ የላቀ ነው ማለት ነው። መቶ መሙያውንም "ላኢላሃ ኢለላሁ ወሕደሁ ላሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር" ያለ ሰው ‐ ትርጉሙም፦ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም። ብቸኛና አጋር የለውም። ጥራት የተገባው አላህ በምሉዕ ንግስና የተለየና ከርሱ ውጪ ያሉት የማይገባቸውን ውዳሴና ሙገሳ ከውዴታና ልቅና ጋር የተገባው ነው። እርሱም ምንም የማይሳነው ቻይ ነው። እነዚህን ቃላት ያለ ሰው ወንጀሉ ባህር በሚናወጥና በሚላተም ሰአት ከላይ በሚሆነው ነጭ አረፋ ልክ ቢበዛ ራሱ ትማራለችም ትሰረዛለችም።