ከዐብደላህ ቢን ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህን መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው: "ከናንተ መካከል ለጁሙዓ ሶላት የመጣ ሰው ይታጠብ።"» ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።