ዐብደላህ ቢን መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - {በእርሱም ውስጥ (ከትክክለኛ መንገድ) በመዘንበል በዳይ ሆኖ (ማንኛውንም ነገር) የሚፈልግ ሰው ከአሳማሚ ቅጣት እናቀምሰዋለን።} [አልሐጅ: 25] በሚለው የአላህ ቃል ዙሪያ እንዲህ ማለታቸውን ገለፀ: "አንድ ሰው በሐረም መካ ላይ በምላስ ወይም ሆን ብሎ በመግደል አላህ እርም ያደረገው በሚደፈርበት መልኩ መጥፎን ስራ ለመስራት በነፍሱ ቢያስብና ቢቆርጥ ይህን ሊያደርግ የቆረጠው በየመን ከሚገኘው የዓደን ከተማ ሆኖ ቢሆንና ባይሰራው እንኳ በዚህ ምክንያት አላህ በአሳማሚ ቅጣቱ ሊቀጣው የተገባ ይሆናል። ለዚህ ቅጣት ማሰቡ ብቻ በቂ ነው።"