ከአቡ ሙሳ አልአሽዐሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና-እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፡ "ሁለቱን የቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት የሰገደ ሰው ጀነት ገባ።" ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሁለቱን የቀዝቃዛ ወቅቶች ሶላት ለመስገድ በመጣር ላይ አነሳሱ። እነሱም: የፈጅርና የዐስር ሶላቶች ናቸው። በጊዜው፣ በጀመዓና ሌሎቹንም የሶላት ሐቆች አሟልቶ እነዚህን ሶላቶች የሰገደ ሰውን ጀነት መግቢያ ሰበብ እንደሚሆኑት በመንገር አበሰሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የፈጅርና የዐስር ሶላት ላይ መጠባበቅ ያለውን ትሩፋት እንረዳለን። የፈጅር ሶላት ጣፋጭ እንቅልፍ የሚኖርበት ወቅት ሲሆን ዐስር ደግሞ ሰዎች በስራ የሚጠመዱበት ወቅት ነው። እነዚህን ሶላቶች ተጠባብቆ የሰገደ ሰው ሌሎቹንም ሶላቶች ተጠባብቆ መስገዱ አይቀርም።
  • የፈጅርና የዐስር ሶላት በቀዝቃዛ ወቅት የተሰየሙት የፈጅር ሶላት የምሽት ቅዝቃዜ ያለባት ወቅት ስለሆነ ሲሆን የዐስር ሶላት ደግሞ የቀኑ ቅዝቃዜ ስላለባት ነው። በሙቀት ወቅት ብትሆንም እንኳ ሙቀቷ ከርሷ በፊት ካለው ሙቀት አንፃር ቀዝቀዝ ያለ ነው። ወይም በዚህ የተሰየመው በማቆራኘት መልኩ ነው። ልክ ለፀሀይና ለጨረቃ ሁለቱ ጨረቃዎች እንደሚባለው ማለት ነው።