ከጃቢር ቢን ዐብደላህ ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል: "በድርና ሑደይቢያ ላይ የተሳተፈ ሰው እሳት አይገባም።"» ሶሒሕ ነው። - رواه أحمد وأصله في صحيح مسلم
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በሂጅራ በሁለተኛው ዓመት የተካሄደችውን የበድር ዘመቻ ከነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ጋር ሆኖ ለመዋጋት የተሳተፈና በስድስተኛው አመተ ሂጅራ የተከሰተችውን የውዴታው ቃልኪዳን የነበረበትን የሑደይቢያን ስምምነት የተሳተፈ ሰው እሳት እንደማይገባ ተናገሩ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ይህ ሐዲሥ የበድርና የሑደይቢያ ተሳታፊዎችን ደረጃ ያስረዳናል። እነርሱም እሳት አይገቡም።
  • አላህ እነርሱን ከበዳይነት (ሊጠብቃቸው) ኃላፊነት እንደወሰደላቸው፤ በኢማን ላይ መሞትን እንደሚገጥማቸው፤ የእሳት ቅጣት ሳይነካቸውም ጀነት እንደሚያስገባቸው መገለፁን እንረዳለን። ይህም አላህ ለሻው የሚሰጠው የአላህ ችሮታ ነው። አላህ የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።