ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህ ለኡመታቸው በሶስት ሁኔታዎች ላይ እያሉ የሰሩትን ወንጀል ይቅር እንዳለ ተናገሩ:- የመጀመሪያው: በስህተት: ማለትም ሆነ ብለው ሳይሆን የሰሩት ወንጀል ማለት ነው። ይህም ማለት አንድ ሙስሊም በድርጊቱ አንዳችን ነገር ማሰቡና ድርጊቱ ግን ካሰበው ውጪ ሆኖ መገኘቱ ነው። ሁለተኛው: በመርሳት: ይህም ማለት አንድ ሙስሊም አንድን ነገር ለመስራት ያስባል። ነገር ግን ድርጊቱን ለመስራት ባሰበበት ወቅት ይረሳዋል። በዚህም ወንጀል አይኖርበትም። ሶስተኛው: በመገደድ ነው። አንድ ባሪያ መስራት ሳይፈልግና አስገዳጁንም አካል መከላከል በማይችልበት ሁኔታ ላይ ሆኖ ተገዶ አንድን ድርጊት ሊሰራ ይችላል። በዚህ ጊዜ በርሱ ላይ ወንጀል ወይም ጣጣ አይኖርበትም። የሐዲሡ ሃሳብ ግን በባሪያና በጌታው መካከል የተከለከለን በመስራት ላይ መርሳትን የሚመለከት ነው። ትእዛዝን ረስቶ ቢተው ግን ትእዛዙ አይነሳለትም። እነዚህን ነገሮች ተከትሎ የተከሰተ ወሰን አላፊነት ካለ የፍጡርም ሐቅ አይነሳለትም። በስህተት የገደለ ሰው ለምሳሌ በርሱ ላይ ጉማ ይኖርበታል። ወይም በስህተት መኪና ቢያጠፋ በርሱ ላይ መኪናውን መክፈል አለበት።