ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: «የትንሳኤ ቀን በሰዎች መካከል መጀመሪያ የሚፈረደው ጉዳይ የደም ጉዳይ ነው።» ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የትንሳኤ ቀን በሰዎች መካከል መጀመሪያ የሚፈረደው ጉዳይ ከፊሉ ከፊሉን የሚበድልበት በሆነው እንደመግደልና ማቁሰል ያሉ የደም ጉዳዮች መሆኑን አወሱ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • የደም ጉዳይ ከባድ መሆኑን እንረዳለን። ፍርድ የሚጀመረው በአንገብጋቢው ጉዳይ ነውና።
  • ወንጀሎች የሚተልቁት በርሱ ምክንያት የሚከሰቱ ብክለቶች እንደመተለቃቸው መጠን ነው። ንፁህ ነፍስን ማጥፋት ደግሞ ከትላልቅ ብክለቶች መካከል አንዱ ነው። በአላህ ማጋራትና ኩፍር (ክህደት) እንጂ ምንም ከርሱ የሚከፋ ወንጀልም የለም።