ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የእስልምና ሃይማኖት በሁሉም ጉዳዮች በገርነትና በማቅለል ላይ የተገነባ መሆኑን ገለፁ። አለመቻልና አስገዳጅ ምክንያቶች ሲኖሩም ገርነቱ ይጨምራል። በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ከአቅም በላይ መጥለቅና ገራገርነትን መተውም መጨረሻው አለመቻልና ሁሉንም ወይም የተወሰነውን ስራ ማቋረጥ ነው ቀጥለውም ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ወሰን ሳያልፉ ሚዛናዊ በመሆን ላይ አነሳሱ። አንድ ባሪያ ከታዘዘበት ነገር ማጓደል አይኖርበትም፤ የማይችለውንም ለመስራት አይጫንበትም። ሙሉ ለሙሉ መስራት ካቃተው ወደ ሙሉነት ቀረብ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ገለፁ። ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስራን አሟልቶ መስራት ያቃተው ሰው ብታንስ እንኳ ዘውታሪነቷን ለማስቀጠል የምትሠራ ሥራ ትልቅ ምንዳ እንደምታስገኝ አበሰሩ። አለመቻል በራሱ ድክመት የመጣ እስካልሆነ ድረስ የምንዳ መጉደልን አያስከትልምና። ዱንያ እውነታዋ ወደ መጪው ዓለም የምንጓዝበት የጉዞና የመሸጋገሪያ ሀገር እንደመሆኗ መጠን ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አምልኮን ነቃ በሚያደርጉ ሶስት ወቅቶች ላይ ዘውትረን በመፈፀም እንድንታገዝ አዘዙ። የመጀመሪያው: የማለዳ ጉዞ ነው: ይህም በመጀመሪያው የቀን ክፍል በማምለክ ነው። ወቅቱም በፈጅር ሶላትና በፀሐይ መውጣት መካከል አምልኮን መፈፀም ማለት ነው። ሁለተኛው: ከዝሁር በኋላ የቀትር ጉዞ ነው። ሶስተኛው: የሌሊቱን ሁሉ ወይም የተወሰነው ክፍል ላይ የሌሊት ጉዞ ነው። የሌሊት ስራ ከቀን ስራ የሚከብድ ስለሆነ "የተወሰነ ከሌሊትም" በማለት የተወሰነውን ሰአት ብቻ እንድናመልክበት አዘዙ።