ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "አንዳችሁ ያዛጋ ጊዜ ሸይጧን ወደ ውስጡ ስለሚገባ በእጁ አፉን ይያዝ።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በስንፍና ወይም በጥጋብና በመሳሰሉት ምክንያት ሲያዛጋ አፉን የከፈተ ሰው ክፍት እንደሆነ ከተወው ሸይጧን ወደ ውስጡ ይገባልና እጁን አፉ ላይ በማኖር እንዲዘጋው ተናገሩ። እጁን አፉ ላይ ማኖሩ ሲያፋሽግ ሸይጧን እንዳይገባ ይከላከላልና።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • አንድ ሰው ማዛጋት የፈለገ ጊዜ በቻለው መጠን አፉን መክደን አለበት። ይህም አፉ እንዳይከፈት አፉን ተቆጣጥሮ እንደተዘጋ እንዲቀር በማድረግ ነው። አፉ እንደተዘጋ ማስቀረት ካልቻለም እጁን አፉ ላይ በማኖር በእጁ አፉን መሸፈን ነው።
  • በሁሉም ሁኔታዎች ኢስላማዊ ስነ-ስርዓቶችን መጠበቅ ይገባል። ይህም የሙሉነትና የስነምግባር መገለጫ ስለሆነ ነው።
  • ሸይጧን ወደ ሰው ልጅ ከሚገባበት ቀዳዳ ባጠቃላይ መጠንቀቅ ይገባል።