ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሚንበራቸው ላይ ሆነው ጁመዓን ያለምንም ተቀባይ ምክንያት በስንፍናና በማቃለል ከመተውና ከርሱ ወደኃላ ማለትን አስጠነቀቁ። ያለበለዚያ ግን አላህ በልቦቻቸው ላይ እንደሚያሽግና እንደሚሸፍን፤ በቀልባቸው ላይ እውነትን ከመከተል የሚያቅብ ግርዶሽ እንደሚያደርግና ከዚያም ከመልካም መንገዶች ከሚዘናጉትና ነፍሳቸውም ከአምልኮ ቸልተኛ ከሆኑት እንደምትሆን ተናገሩ።