ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሙስሊም ወንድም በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እንዲረዳ አዘዙ። አንድ ሰውዬም እንዲህ አለ: የአላህ መልክተኛ ሆይ! ተበዳይ በሆነ ጊዜ በደልን ከርሱ ላይ በማስወገድ እረዳዋለሁ። ንገሩኝ እስኪ በዳይ ከሆነ እንዴት ነው የምረዳው? እርሳቸውም እንዲህ በማለት መለሱ: ከበደል ትከለክለዋለህ፣ እጁን ትይዘዋለህ፣ ትገታዋለህ፣ ታቅበዋለህ። ይህ በሰይጣኑና በመጥፎ በምታዘው ነፍሱ ላይ እያገዝከው ነው።