አቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ተወዳጁና ባልደረባው የሆኑት ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሶስት ነገሮች አደራ እንዳሏቸውና ቃልኪዳንም እንዳስገቧቸው ተናገሩ: የመጀመሪያው: ከሁሉም ወር ሶስት ቀናትን መጾም ነው። ሁለተኛው: በየቀኑ ሁለት ረከዓ ዱሓ መስገድ ነው። ሶስተኛው: ከመተኛት በፊት ዊትር መስገድ ነው። ይህ ግን የሌሊቱ መጨረሻ ላይ አልነቃም ብሎ ለፈራ ነው።