ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የረመዿን ወር መግቢያና መውጫን ምልክት ገለፁ። እንዲህ አሉ: የረመዿንን ጨረቃ ያያችሁ ጊዜ ፁሙ። በናንተና በጨረቃው መካከል ደመና ከገባና ከጋረዳችሁ ደሞ የሸዕባንን ወር ሰላሳ አድርጋችሁ ቁጠሩ። የሸዋልን ጨረቃ ያያችሁ ጊዜ ፆም ፍቱ። በናንተና በጨረቃው መካከል ደመና ከገባና ከጋረዳችሁ የረመዿንን ወር ሰላሳ አድርጋችሁ ቁጠሩ።