ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በአኳኋኑም ይሁን በቀለሙም፣ በአይነቱም ይሁን በአለባበስ መንገዱም፣ በመዋቢያነቱ (ማስጌጫዎች)ና በመሳሰሉ መንገዶች ሴት ልጅ የተለየችበት በሆነ ልብስ የሚመሳሰል ወንድ ላይ ከአላህ እዝነት እንዲባረርና እንዲርቅ ዱዓእ አድርገዋል። ወይም ልክ እንደዚሁ ወንድ ልጅ በተለየበት ልብስ የምትመሳሰል ሴት ልጅ ከአላህ እዝነት እንዲባረሩና እንዲርቁ ዱዓ አደረጉ። ይህም ከትላልቅ ወንጀሎች የሚመደብ ከባድ ወንጀል ነው።