ከአማኞች እናት ከዓኢሻህ (ረዲየሏሁ ዓንሃ) -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉ: "በሩብ ዲናርና ከዛ በላይ በሚያወጣ (ስርቆት) እጅ ይቆረጣል።"» ሶሒሕ ነው። - ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የአንድ ዲናር ሩብ እና ከዚህ በላይ የሚያወጣን ነገር የሰረቀ ሌባ እጁ እንደሚቆረጥ ገለፁ። ዋጋውም በንፁህ ወርቅ የ 1.06 ግራም ዋጋን ይመዝናል።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ስርቆት ከትላልቅ ወንጀሎች የሚመደብ ነው።
  • አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ የሌባን ቅጣት ወስኗል። እርሱም እጁን መቁረጥ ነው። አላህ እንዲህ እንዳለው {ሰራቂውንና ሰራቂይቱንም እጆቻቸውን ቁረጡ።} [አልማኢዳህ:38] የነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሱናም የሚቆረጥበትን መስፈርቶች አብራርቷል።
  • ሐዲሡ ውስጥ እጅ በማለት የተፈለገው መዳፍን ሲሆን በርሱና በክንዱ መካከል ከሚለየው አጥንት መቁረጥ ነው።
  • የሌባን እጅ የመቁረጡ ጥበብ የሰዎችን ገንዘብ መጠበቅና ሌሎችን ወሰን አላፊዎች ማስጠንቀቅ ነው።
  • ዲናር ማለት አንድ ሚሥቃል ወርቅ ነው። በዚህ ዘመንም በ24 ካራት ወርቅ (4.25 ግራም) ይመዝናል። የአንድ ዲናር ሩብም አንድ ግራም ከተወሰነ ሚሊ ግራም ይመዝናል።
explain-icon

ተጨማሪ