አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ፦ "ቀድሞ ቀመስን በመቀነስ፣ ጥፍርን በመቁረጥ፣ የብብት ፀጉርን በመንጨትና ብልት አካባቢ የሚበቅልን ፀጉር በመላጨት ዙሪያ ከአርባ ቀናት በላይ ሳናስወግድ እንዳንተወው የጊዜ ገደብ ተቀመጠልን።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።
explain-icon

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ወንድ ልጅ ቀድሞ ቀመሱን ለመቀነስ፣ የእጆችና እግሮችን ጥፍሮች ለማሳጠር፣ የብብትን ፀጉር ለመንጨትና ብልት አካባቢ የሚበቅለውን ፀጉር ለመላጨት ከአርባ ቀናት በላይ ሳይቆረጥ እንዳይተው የጊዜ ገደብ አስቀመጡ።

explain-icon

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  • ሸውካኒይ እንዲህ ብለዋል: "ተመራጩ አቋም የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመጠኑት አርባ ቀን ይገደባል የሚለው ነው። ከዚህ በላይ ማሳለፍም አይፈቀድም። እየረዘመ እንኳ ይህ የጊዜ ገደብ እስኪጠናቀቅ ማሳጠርና መላጨት የተወ ሰው ሱናን ተፃራሪ ተደርጎ አይቆጠርም።"
  • ኢብኑ ሁበይራ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ይህንን የማዘግየት የመጨረሻው ቀነ ገደቡ ነው። የተሻለው ግን ይህንን የመጨረሻ ቀነ ገደብ ሳይደርስ በፊት መቁረጥ ነው።"
  • እስልምና ንፅህና፣ መፅዳትና ውበት ላይ ትኩረት ማድረጉን እንረዳለን።
  • ቀድሞ ቀመስን ማሳጠር የሚፈፀመው የላይኛው ከንፈር ላይ የሚበቅልን የተወሰነን ፀጉር በመቁረጥ ነው።
  • የብብትን ፀጉር መንጨት የሚፈፀመው ብብት ላይ የሚበቅልን ፀጉር በማስወገድ ነው። ብብት የሚባለውም በጡንቻና በትከሻ መካከል የሚለየው አጥንት ስር የሚገኝ ስፍራ ነው።
  • የብልት ፀጉርን መላጨት ማለት በወንድም ይሁን በሴቶች ብልት ዙሪያ የሚበቅልን ሸካራ ፀጉር መላጨት ማለት ነው።