ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና የተለያዩ የገንዘብ አይነቶችንና የትንሳኤ ቀን ዘካቸውን ያላወጣ ሰው ምንዳ ምን እንደሆነ ገለፁ። የመጀመሪያው: ወርቅ፣ ብርና በነርሱ ደረጃ ያለ ገንዘብና መገበያያ ሸቀጥ ነው። ይኸውም ዘካ ግዴታ ሆኖበት ያልወጣለትን ወርቅና ብር ነው። የትንሳኤ ቀን ሲሆን በዝርግ መልኩ የሚቃጠልም የሚቀልጥም ይደረጋል። በጀሃነም እሳት ውስጥም ትቀጣጠላለች በርሷም ባለቤቱ ይቀጣበታል። በርሷም ጎኑም፣ ግንባሩና ጀርባውም ይተኮሳል። በቀዘቀዘች ቁጥር ግለቷ ይመለሳል። አላህ በፍጡራን መካከል ፈርዶ ከጀነት ነዋሪዎች ወይም ከእሳት ነዋሪዎች መካከል ከአንዱ እስኪሆን የአንዱ ቀን መጠን ሀምሳ ሺህ አመት የሚያህል በሆነበት የእለተ ትንሳኤ ሙሉ ጊዜው በዚህ ሁኔታ ቅጣቱ ይቀጥላል። ሁለተኛው: ግዴታ የሆነው ዘካዋንና ሐቋን ያልተወጣላት የግመል ባለቤት ነው። ከግመል ሐቅም እርሷ ዘንድ ለሚገኙ ድሆች በማለብ ማጠጣት ነው። ይህቺ ግመልም ተልቃ፣ ሰብታና ከነበሩበት ቁጥር በዝተው ይመጣሉ። የትንሳኤ ቀን የተስተካከለ ሰፊ መሬት ላይ ባለቤቱ ይዘረጋል፣ ይጣላል፣ ለርሷ ይለጠጣል። በእግሮቻቸውም ይረገጣል፣ በጥርሶቻቸውም ይነከሳል። የመጨረሻዋ ግመል ባለፈች ቁጥር የመጀመሪያው ይመለሳል። አላህ በፍጡራን መካከል ፈርዶ ከጀነት ነዋሪዎች ወይም ከእሳት ነዋሪዎች መካከል ከአንዱ እስኪሆን ድረስም የአንዱ ቀን መጠን ሀምሳ ሺህ አመት የሚያህል በሆነበት በእለተ ትንሳኤ ሙሉ ጊዜውን በዚህ ሁኔታ ቅጣቱ ይቀጥላል። ሶስተኛው: ግዴታ የሆነበትን ዘካ የማያወጣለት የከብት፣ የፍየልና የበግ ባለቤት የሆነ ሰው ነው። ከነበሩበት መጠን ምንም ሳይቀነስ በዝተው ይመጣሉ። የትንሳኤ ቀን የተስተካከለ ሰፊ መሬት ላይ ባለቤቱ ተዘርግቶ ይጣላል፣ ለርሷ ይለጠጣል። ከነርሱም መካከል ቀንዱ የተጠመዘዘ፣ ቀንድ የሌለውና ቀንዱ የተሰበረ አይኖርም። ይልቁንም የተሟላ ባህሪ ተላብሰው ነው የሚመጡት። በቀንዶቻቸውም ይወጉታል፣ በእግራቸውም ይረግጡታል። የመጨረሻዋ ባለፈች ቁጥር የመጀመሪያዋ ትመለሳለች። አላህ በፍጡራን መካከል ፈርዶ ከጀነት ነዋሪዎች ወይም ከእሳት ነዋሪዎች መካከል ከአንዱ እስኪሆን ድረስ የአንዱ ቀን መጠን ሀምሳ ሺህ አመት የሚያህል በሆነበት በእለተ ትንሳኤ ሙሉ ጊዜውን በዚህ ሁኔታ ቅጣቱ ይቀጥላል። አራተኛው: ፈረስ የሚያደልብ ነው። ይህም ሶስት አይነት ናቸው። አንደኛ: እርሷ ለርሱ ወንጀል የሆነችበት ናት። ይህም ለይዩልኝ፣ ለፉከራና ሙስሊሞችን ለመዋጋት የያዛት እንደሆነ ነው። ሁለተኛ: እርሷ ለርሱ የምትሸሽገው የሆነች ናት። ይህም በአላህ መንገድ ለመዋጋት የያዛት እንደሆነ ነው። ከዚያም ለፈረሷ በመቀለብ፣ ጣጣዋን በመቻል ከዚህም ውስጥ ኮርማዋን በማዘጋጀት ለርሷ መልካም የዋለ እንደሆነ ነው። ሶስተኛ: እርሷ ለርሱ ምንዳ የምታስገኝ የሆነች ናት። ይህም በአላህ መንገድ ለሙስሊሞች ለመዋጋት የያዛትና በቡቃያ ስፍራና በጨፌ ውስጥ ያሰማራት እንደሆነ ነው። ይህቺ ፈረስ አንድም አትበላም ለርሱ በበላችው ቁጥር ምንዳ ቢፃፍለት እንጂ፤ በእበቷና ሽንቷ ቁጥር ልክ ምንዳ ቢፃፍለት እንጂ፤ የምትታሰርበትን ገመድ ቆርጣ በምድር ከፍታ ላይ አትሮጥም አላህ ለርሱ በኮቴዋና እበቷ ቁጥር ልክ ምንዳን ቢፅፍለት እንጂ፤ ባለቤቱ እርሷን ይዞ በወንዝ በኩል ሲያልፍ እርሷን ማጠጣት ሳይፈልግም አትጠጣም አላህ በጠጣችው ቁጥር ለርሱ ምንዳ የሚፅፍለት ቢሆን እንጂ። ቀጥሎ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለአህያ እርሷም እንደ ፈረስ አምሳያ ናትን? ተብለው ተጠየቁ። እርሳቸውም: ከዚህች አጭር ከሆነችው አንቀፅ በቀር እርሷን የሚመለከት አንቀፅ አልወረደም። ይህቺ አንቀፅም ሁሉንም የአምልኮና የወንጀል አይነቶችን የምታጠቃልል ናት። ይህቺም አንቀፅ {የብናኝ ክብደት ያክልም መልካም የሰራ ሰው ያገኘዋል። የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሰራ ሰው ያገኘዋል።} [አዝዘልዘላህ:8] የምትለዋ የአላህ ንግግር ናት። አህያን ሲያደልብ አላህን ለመታዘዝ አልሞ ከሆነ የዚህን ምንዳ ያገኛል። ወንጀል ከሰራ ደግሞ የዚህን ቅጣት ያገኛል። ይህ አንቀፅ ሁሉንም ስራዎች የሚጠቀልል ነው።