ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - አማኝ የሆነ ሰው በዱንያ ትእዛዛትን በመፈፀምና ክልከላን በመራቅ በኩል ሸሪዓዊ በሆኑ ሃላፊነቶች ስለታሰረ የዱንያ ህይወት ለአማኝ እስር ቤት እንደሆነች እና ከዚህም ሲሞት አላህ ለርሱ ወዳዘጋጀለት ዘውታሪ ፀጋ ተሸጋግሮ እንደሚያርፍ ተናገሩ። ከሃዲ የሆነ ሰው ደግሞ ነፍሱ የፈለገችውን ሁሉና ዝንባሌው የመራውን ሁሉ ስለሚሰራ ዱንያ ለከሃዲ ጀነት መሆኗንና ሲሞትም አላህ የትንሳኤ ቀን ወዳዘጋጀለት ዘውታሪ ቅጣት ይሸጋገራል ብለው ተናገሩ።