የነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሚስትና የአማኞች እናት ከሆነችው ከኡሙ ሰለማ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉ: "ለርሱ (ለኡዱሒያ) የሚታረድ እርድ ያለው ሰው የዙልሒጃ ጨረቃ የወጣች ጊዜ ኡዱሒያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩም ይሁን ከጥፍሩ አንዳችም እንዳይቆርጥ።" ሶሒሕ ነው። - ሙስሊም ዘግበውታል።